Bench Sheko Zone Transport and Road Dev't Department

Bench Sheko Zone Transport and Road Dev't Department Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Bench Sheko Zone Transport and Road Dev't Department, Mizan, Mizan Teferi.

በቤንች ሸኮ ዞን ትራንስፖርት እና መንገድ ልማት መምሪያ በደቡብ ቤንች ወረዳ ውስጥ ያሉ የመንገድ ልማት ስራዎችን ገበኘ።    የካቲት 21/2017ዓ.ም ደ/ወርቅ:  በቤንች ሸኮ ዞን ትራንስፖ...
28/02/2025

በቤንች ሸኮ ዞን ትራንስፖርት እና መንገድ ልማት መምሪያ በደቡብ ቤንች ወረዳ ውስጥ ያሉ የመንገድ ልማት ስራዎችን ገበኘ።

የካቲት 21/2017ዓ.ም ደ/ወርቅ: በቤንች ሸኮ ዞን ትራንስፖርት እና መንገድ ልማት መምሪያ ሀላፊ አቶ አበበ ኑራ የተመራ ቡንድን በደቡብ ቤንች ወረዳ ውስጥ የተሰሩ ያሉ አጠቃላይ የመንገድ ልማት ስራዎች ላይ ምልከታ አድርጓል ።

በመንገድ ልማት ስራዎች ከወረዳው ደ/ወርቅ ከተማ እስከ ጊጪ ያለው 19ኪ.ሜ የመንገድ ጥገና ስራዎች ፣ ጃንቹ ቀበሌን ከአይናምባ ቀበሌ የሚያገናኘውና በመገንባት ላይ ያለው የዛን ወንዝ ድልድይ እና በክልል ገጠር መንገድ በጀት ግንባታው ተጀምሮ የተቋረጠው የጌዱ ቀበሌ ዚብን ወንዝ ድልድይ ግንባታ ላይም ምልከታ ተደርጓል ።

በምልከታው ላይ የቤንች ሸኮ ዞን ትራንስፖርት እና መንገድ ልማት መምሪያ ሀላፊ አቶ አበበ ኑራ እና የወረዳው ትራንስፖርት እና መንገድ ልማት ጽ/ቤት ተወካይ ሀላፊ አቶ ሰለሞን ጸሀፊን ጨምሮ የዞን እና የወረዳው ትራንስፖርት እና መንገድ ልማት ተቋማት ባለሞያዎ ተገኝተዋል ።

ወረዳው በመንግሥት እና በህብረተሰቡ ተሳትፎ ትልቅ በጀት መድቦ ሰፊ የመንገድ ጥገና እና ከፈታ ስራዎች ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መገኘቱ የሚደነቅ መሆኑን የቤንች ሸኮ ዞን ትራንስፖርት እና መንገድ ልማት መምሪያ ሀላፊ አቶ አበበ ኑራ በጉብኝቱ ወቅት ተናግረዋል ።

የመምሪያ ሀላፊው አክለውም በወረዳው ውስጥ በተለያዩ የበጀት ምንጮች እየተሰሩ የቆሙ የመንገድ ጥገና እና ድልድይ ግንባታዎች ተጠናቀው አገልግሎት እንዲሰጡ ከሚመለከታቸው አካላት ተነጋግሮ እልባት እንዲያገኙ የማድረጉ ስራ እና የዞኑም ድጋፍና ክትትል ተግባርም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል ።

የወረዳው ትራንስፖርት እና መንገድ ልማት ጽ/ቤት ተወካይ ሀላፊ አቶ ሰለሞን ጸሀፊ በበኩላቸው በዞኑ ትራንስፖርት እና መንገድ ልማት መምሪያ ባለድርሻ አካላት በምልከታው ወቅት መሻሻል አለባቸው ተብለው የተሰጡትን ግብረ መልሶች ተቀብለው ተግባራዊ ለማድረግ ከመቼውም ጊዜ በላይ በትኩረት እንደሚሰራ ገልጸዋል ።
ምንጭ:- ደቡብ ቤንች ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን ጽ/ቤት

የቤንች ሸኮ ዞን  ትራንስፖርት እና መንገድ ልማት መምሪያ በሸኮ ወረዳ እየተከናወኑ ለሚገኙት የመንገድ መሰረተ ልማቶች ስራ የሚውል የ250 ሺህ ብር ድጋፍ አደረገ!!!===============...
26/02/2025

የቤንች ሸኮ ዞን ትራንስፖርት እና መንገድ ልማት መምሪያ በሸኮ ወረዳ እየተከናወኑ ለሚገኙት የመንገድ መሰረተ ልማቶች ስራ የሚውል የ250 ሺህ ብር ድጋፍ አደረገ!!!
==========================
የካቲት 19/2017ዓ/ም
በወረዳው እየተከናወኑ ያሉትን የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎችን የጎበኘው የቤንች ሸኮ ዞን መንገድ ትራንስፖርት መምሪያ ለልማቱ የ250 ሺህ ብር ድጋፍ አድርጓል ።

በቤንች ሸኮ ዞን ትራንስፖርትና መንገድ ልማት መምሪያ ኃላፊ በአቶ አበበ ኑራ የተመራው የመምሪው ማኔጅመንት ልዑካን በወረዳው እየተከናወኑ የሚገኙትን የመንገድ መሰረት ልማት ስራዎችን ጎብኝቷል።

ልዑካኑ የዳማ ወንዝ ድልድይ ግምባታ ስራ ያበትን ደረጃ እና ከጎሚቃ ሙሩንስ እየተሰራ የሚገኘውን የመንገድ ስራ ላይ ምልከታ አካሂዷል ።

በሸኮ ወረዳው እና ሸኮ ከተማ አስተዳደር በመንግስትና ህብረተሰቡ ተሳትፎ በርካታ መሰረተ ልማቶች እየተከናወነ ይገኛል።

በጉብኝቱ የዳማ ወንዝ ድልድይ ግምባታ ስራ ከ92 በመቶ ላይ መድረሱ ተጠቁሟል።

ግምባታውን እስከ የካቲት መጨረሻ ላይ ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ ተጠቁሟል ።

በኩች ተቋራጭ መንገድ ስራዎች ማህበር እያካሄደ የሚገኘውን ግምባታ ስራ የዳማ ወንዝ ድልድይ ግምባታ ስራ አስኪያጅ አቶ እሸቱ ለልዑካኑ ገለጻ አድርገዋል ።

የመልካም አስተዳደር ችግር ከመሆን ተላቆ የኢኮኖሚ ፣የእድገት እና የብልጽግና መሰረት እንዲሆን ህዳር 6 ቀን 2016ዓ/ም የመሰረተ ድንጋይ የተቀመጠለት የዳማ ወንዝ ሊጠናቀቅ የመጨረሻ ምዕራፍ ላይ ይገኛል ።

በመንግስትና በህብረተሰቡ ተሳትፎ እየተገነባ የሚገኘው የዳማ ወንዝ ድልድይ በወረዳው የ350 ሚሊየን ብር ፕሮጀክት አካል መሆኑን የገገለጹት የቤንች ሸኮ ዞን መንገድ ትራንስፖርት መምሪያ ኃላፊ አቶ አበበ ኑራ እንደገለጹት ድለድዩ ስራ መልካም አፈጻጸም ላይ በመገኘቱ መደሰታቸውን ገልጸዋል።

የሸኮ ወረዳ በተፈጥሮ ጸጋ የታደለ ሃብታም ወረዳ መሆኑን የገለጹት አቶ አበበ ሀብቶችን በአጭር ጊዜና ገበያ በማቅረብ በኢኮኖሚ የበለጸገ ማህበረሰብ እንዲፈጠር በማድረግ ረገድ ድልድዩ ያለው ፋይዳ ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል።

ድልድዩ በአግባቡና በወቅቱ ተጠናቆ አገልግሎት እንዲሰጥ ክትትልና ቁጥጥር ስራዎች ሲካሄዱ መቆየታቸውን የጠቆሙት አቶ አበበ ተመርቆ አገልግሎት እንዲሰጥ የመምሪው ክትትልና ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል ።

የዳማ ወንዝ በዞኑ ትልቁና ረጅሙ ድልድይ መሆኑን ገልጸው 22 ሜትር ርዝመት ፣ 11.8 ሜትር ቁመትና ለግንባታው 22 ሚሊየን ብር ወጪ እየተገነባ የሚገኝ ፕሮጀክትን የጎበኙት የመምሪያው ማኔጅመንት አባላት ድልድዩ የደረሰበት ደረጃ እንዳስደሰታቸው በመጠቆም የኮንክሪት ሙሌት ስራ ላይ በመገኘት ከሙያዊ ድጋፍ ባሻገር በጉልበት ስራ ጭምር ለማገዝ ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል ።

የፕሮጀክቱ ስራ አስኪያጅ አቶ እሸቱ በላይ ድልድዩ በጊዜ እንዲጠናቀቅ የወረዳው መንግስት ለመሰረት ልማቱ እያደረገ ያለው ድጋፍና ትኩረት ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመው ቀሪ የመጨረሻ ምዕራፍ ስራዎችን በአጭር ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።የግምታ ስራውም 92 በመቶ መድረሱን አክለዋል ።

በተያያዘ ዜና ልዑካኑ ጎሚቃ፣ጉፊቃና ሙሩንስ ቀበሌዎችን የሚያገናኘው በህብረተሰቡ ተሳትፎ እየተገነባ የሚገኘው 19 ኪሎ ሜትር መንገድ ግንባታ ስራን የጎበኘ ሲሆን ለልማቱ 250 ሺህ ብር ድጋፍ አድርጓል ።

የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሪ ጉርሙ እንደገለጹት መምሪያው በወረዳው ተገኝቶ የልማት ስራዎችን ተመልክቶ ሙያዊና የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ አመስግነዋል::

26/02/2025
በቤንች ሸኮ ዞን ሼይ ቤንች ወረዳ በ10.4 ሚሊዬን ወጪ የሚጠገን የከሽታ መንገድ ሳይት ርክክብ ተደረገሼይ ቤንች "ሲዝ "(የካቲት 19/2017ዓም)በክልሉ የገጠር  ትስስር ለምግብ ዋስትና (...
26/02/2025

በቤንች ሸኮ ዞን ሼይ ቤንች ወረዳ በ10.4 ሚሊዬን ወጪ የሚጠገን የከሽታ መንገድ ሳይት ርክክብ ተደረገ

ሼይ ቤንች "ሲዝ "(የካቲት 19/2017ዓም)በክልሉ የገጠር ትስስር ለምግብ ዋስትና (RCAP- RCFS) ፕሮግራም ድጋፍ በ10.4 ሚሊዬን ወጪ የሚጠገን የከሽታ መንገድ ሳይት ርክክብ ተደርጓል።

የሳይት ርክክቡ "ኃይሌ ገብሬ ጠቅላላ ተቋራጭ" ለሚባለው የተደረገ ሲሆን በርክክቡ የሼይ ቤንች ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ እንደገለጹት መንገዱ ዚያጊን እና ከሽታን የሚያቋርጥ 12 ኪ/ሜ ነው የጥገና ሥራውም ለህብረተሰቡ ዘላቂ ግልጋሎት መስጠት እንዲችል በጥራትና በጊዜ ሊከናውን ይገባል ብለዋል።

ወረዳው የሚጠበቀውን ድጋፍና ክትትል እንደሚያደርግ ገልጸው ዝናብ ከጀመረ ለሥራ መስተጓጎል እና ጫና ስለሚፈጥር ተቋራጩም ከወዲህ ጀምሮ በመግባት የጥገና ሥራ መከወን አለበት ስሉ ጠይቋል።

አቶ ጌዲዮን እስቲፋኖንስ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል የትራንስፖርት እና መንገድ ልማት ቢሮ ም/ል ኃላፊ በበኩላቸው ጨረታውን ያሸነፈው ይህ ተቋራጭ ነው ስራውንም በተገቢው እንዲያከናውን ድጋፍና ክትትል እናደርጋለን የወረዳው ስትሪንግ ኮሚቴም ቀጣይነት ያለ ክትትል ማድረግ አለበት ብለዋል።

ተቋራጩ በአራት ወራት ለማጠናቀቅ ነው ውል የገባው ሆኖም ከዛ ባነሰ ጊዜ እንዲያጠናቅቅ እናበረታታለን ብለዋል።

የተቋራጩ ስራ አስኪያጅ የሆኑት አቶ ኃይሌ ገብሬ እንደገለጹት ወደ ስራ የሚያስገቡን ሁኔታዎች አሉ ስለዚህ ማሽኖችን አስገብተን ወደ ሥራ እንገባለን ስሉ ገልጸዋል።

የጥገና ስራ ከዚያጊን መገቢያ ጀምሮ እስከ ቤስክን ድልድይ ድረስ የሚከናውን ሲሆን በርክክብ መረሃ ግብር የክልልና የዞን ባለ ድርሻ አካላትን ጨምሮ የወረዳ ዋና አስተዳዳሪና የብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት አመራሮች ተገኝቷል።

የተከበሩ አቶ አገኘሁ ወርቁ መልካም የስራ ግዜ እንመኛለን።@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@በነበሮት በትራንስፖርት መንገድ ልማት መምሪያ የስራ ግዚያትተቋሙን ታይቶ በማይታወቅ መልኩ  በማነቃቃ...
01/05/2024

የተከበሩ አቶ አገኘሁ ወርቁ መልካም የስራ ግዜ እንመኛለን።
@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@
በነበሮት በትራንስፖርት መንገድ ልማት መምሪያ የስራ ግዚያት
ተቋሙን ታይቶ በማይታወቅ መልኩ በማነቃቃት በሁለቱም ዘርፍ እስከታቸኛው ማህበረሰብ በመውረድ በተቋሙ ለውጥ እንዲመጣ አድረገዋል፣ ተቋሙን ምቹ የስራ ቦታ እንዲኖረው፣ ከሚመለከታቸው ጋር በመሆን የተለያዩ ግንባታዎች፣ አሰራሮች በማምጣት አነቃቅተዋል። በተላይ የመንገድ ድልድይ ስራዎች በአካል ተገኝቶ የሚያደርጉት ክትትል፣ድጋፍ አመስግነናል።
"በሚሄዱበት መልካም የውጤት ግዜ እንመኛለን።"

ምንም አይነት የተለየ የባጃጅ ታሪፍ አልተጨመረም።@@@@@@@@@@@@@@@@@@@በሚዛን የቤንዝል ግብይትን ምክንያት በማድረግ አንዳንድ የባጃጅ አሽከርካሪዎች አላስፈላጊ የታሪፍ ጭማሪ ያደረጉ ...
01/03/2024

ምንም አይነት የተለየ የባጃጅ ታሪፍ አልተጨመረም።
@@@@@@@@@@@@@@@@@@@
በሚዛን የቤንዝል ግብይትን ምክንያት በማድረግ አንዳንድ የባጃጅ አሽከርካሪዎች አላስፈላጊ የታሪፍ ጭማሪ ያደረጉ መሆኑ ከህብረተሰቡ ጥቆማ የመጣ እንደሚገኝ መምሪያው ገልጿል። የችግሩ ምንጭ አጠቃላይ በከፍተኛ አመራር የሚመራ በኮመቴ የተገመገመ ስለሆነ ዕልባት በቅርቡ ያግኛል። ስለሆነም በከተማችን ከፍተኛ የትራንስፖርት ፍሰት በከተማ ትራንስፖርት እና ወደ ወረዳዎች ለሚንቀሳቀሱ ትራንስፖርት ችግር የሆነ በመሆኑ ጉዳዩ የሚመለከተው አካላት በትኩረት የሰሩ ይገኛሉ።
ስለሆነም የባጃጅ የከተማ ታሪፍ ልዩ ጭማሪ የተደረገ የሌለ መሆኑን እያሳወቅን በተለጠፈው ታሪፍ ውጭ የሚያስከፍሉ የተለያዩ ስነምግባር ችግር የሚያሳዩ ለመንገድ ደህንነት ቡድን መሪ የተሽከርካሪውን ታርጋ እንድታሳውቁ እንገልፃለን። ቁጥጥር የተሰራ ያለ ሲሆን ውስጥ ለውስጥ ተቆጣጣሪዎች በሌሉት የሚከሰተውን ታርጋ በመያዝ ያሳውቁ። ትራፊክ ፣መንገድ ደህንነት በሚጠየቁበት የከፈሉትን ትክክለኛ መረጃ እንዲሰጡ እንጠይቃለን።
0966735937 ታደሰ ከተመረሻ የዞን
0903367478 ጨነቀች የከተማ

የሚዛን አማን የተሽከርካሪ ዕጥረት የተነሳ ህብረተሰቡ በሰዓት ለዕቅዱ ለመድረስ መንገላታቱ የተሽከርካሪ ዕጥረት ምክንያት በማጥናት መፍተሄ የተሰጠ ይገኛል።።@@@@@@@@@@@@@@@በመናሀሪያ ...
16/02/2024

የሚዛን አማን የተሽከርካሪ ዕጥረት የተነሳ ህብረተሰቡ በሰዓት ለዕቅዱ ለመድረስ መንገላታቱ የተሽከርካሪ ዕጥረት ምክንያት በማጥናት መፍተሄ የተሰጠ ይገኛል።።
@@@@@@@@@@@@@@@
በመናሀሪያ ከደረጃ አሰጣጥ ረጃጅም መንገድ መሄድ የሚቸገሩትን ተሽከርካሪ ቀለም ቀይሮ የከተማ ታክስ የተደረገ ይገኛል። አቶ አገኘሁ ወርቁ

በሚዛን አማን ስሚሪት ከግዜ ወደ ግዜ የተገልጋይ ቁጥር የጨመረ የታክሲ ቁጥር የቀነሰ መምጣት በተላይ ሰኞ, ማክሰኞ እንድሁም ቅዳሜ ከፍተኛ ሰልፍ የተስተዋለ መተዋል። ይህንን ለማስተንፈስ ከመናሀሪያ ቅጥቅጥ መኪናዎችን በማስገደድ ፍሰት ማንሳት ላይ ያለን ሲሆን በዚህ ውስጥ ባልተለመደ ባጃጆች ከ30 እስከ 50 ብር ያስከፈሉ መሄድ ከሚገባቸው ኪ.ሜ ውጭ የተጓዙ ለህገ ወጥ ተግባር መሳተፍቸው እና የታክሲን ቁጥር ለመጨመር የተለያዩ መፍተሄ በማዘጋጀት ወደ ትግበራ ተገብቷል።
👉 በቅርብ ግዜ አብዘኛው ባለንብረት ተሽከርካሪውን የተሸጠ የስም ዝውውር የተደረገ ሲሆን የሚዛን አማን ታክሲ ከ70 ወደ 30 መወረዳቸው የፍሰት ቁጥር እንዲጨምር አደርገዋል። በቀጣይ የከተማ ባስ ባለሀብቱን ደግፎ ወደ ተግባር እስኪገባ ህብረተሰቡ በተሽከርካሪ ዕጥረት መንገላታት እንደሌለ በመገምገም የታሪፍ ማሻሻያ ከቀን 30/2016ዓ.ም በማድረግ ከመናሀሪያ በደረጃ አሰጣጥ ረጃጅም ርቀት መሄድ ሚቸገሩትን ቀለም ቀይሮ ወደ ከተማ ማስገባት የተቻለ ነው።
የታሪፍ ጭማሪው ከወር በላይ ጥናት የተደረገ ሲሆን
ከሀገር ሽማግሌ፣ ከተጠቃሚ ግለሰብ፣ ከዞን ፖሊስ፣ከዞን አስተዳደር ጽ/ቤት፣ ከከተማ ፖሊስ፣ ከከተማ ትራንስፖርት ፣ከዞን ትራንስፖርት ከማህበራት የተወጣጣ ኮመቴ ጥናት አድርጎ የተደረሰበት ስምምነት ለመምሪያ ሀላፍ ማቅረብ ችለዋል። ከተገመገመ በሀላ ለዞን ቴክኒክ ኮመቴ ቀርቦ ፀድቋል።
👉 መነሻ የተደረገው:- የመንገድ ሁኔታ፣ የእስፔርፖርት መለዋወጫ ፣ ጓማ፣ መሰል ዕቃዎች ከነበሩበት 300% በላይ መጨመራቸው ታሳቢ በማድረግ የህብረተሰቡን የመክፈል አቅም እንዲሁም ተሽከርካሪዎች ዕጥረት ለመቀነስ ተጨማሪ ተሽከርካሪዎች ለማስገባት ከሚዛን አማን 10 የነበረው 15 ብር፣ከሚዛን ዩኒቨርስቲ 10 ብር ከዩኒቨርስቲ አማን 10 ብር እንዲሆን ቴክኒክ ኮመቴው አፀድቋል።
አሁን ባለው ሁኔታ ከመናሀሪያ በርካታ ተሽከርካሪዎች ቀለም ቀይሮ እንዲገቡ የተደረገ አሁን ባለው ሁኔታ የተሽከርካሪ ቁጥር ማሳደግ ስራ የተሰራ ይገኛል። ተሽከርካሪዎች ከተደረገላቸው ታሪፍ ጭማሬ ውጭ የሚንቀሳቀሱትን ህገ ወጥ ተግባር እንዲቆጠቡ የህግ የበላይ እንዲከበር ለሚመለከተው አካላት እናሳስባለን።

ዕለተ ዕሁድ ከሰዓት👉👉👉👉ሚዛን-አማንምንም የፈዴራል መንገድ ቢሆንም  መንገዱ በጥራት ተጠግኖ ህብረተሰቡን ለርጅም ግዜ እንዲያገልግል ሃላፍነት ይገባችዋል።ክቡር አስተዳዳሪና አስተባባሪው 👉። ...
11/02/2024

ዕለተ ዕሁድ ከሰዓት👉👉👉👉
ሚዛን-አማን
ምንም የፈዴራል መንገድ ቢሆንም መንገዱ በጥራት ተጠግኖ ህብረተሰቡን ለርጅም ግዜ እንዲያገልግል ሃላፍነት ይገባችዋል።
ክቡር አስተዳዳሪና አስተባባሪው 👉።
የዞኑ መንገድ ትራንስፖርት ፣የ ERA ሚዛን ፕሮጀክት ሚዛን ዲስትሪክት፣ እና ሌሎች ፕሮጀክት ማናጅመንቶች በተገኙበት የጥገና ሁኔታ በተደራጀ ከነጥራቱ፣ መቼ ተጀምሮ መቼ እንደሚጠናቀቅ እንዲሁም ማን እንደሚጠግን የተደራጀ ዕቅድ ይቅርብ በማለት በጉብኝት ወቅት አሳስበዋል። የፕሮጀክት አስተባባሪውም ከዞኑ መንግስት ድጋፍ፣ክትትል፣ ፍላጎት ውጭ አንሆንም ከተጋገዝን እንችላለን ብለዋል። በሚቀጥለው ክቡር አስተዳዳሪ በሚሰጠው አቅጣጫ ቀን ዕቅዳቸውን ይዞ ይቀርባሉ። ግን አሁን ለጥገና በተጀመረው የተጓዳ አካል ማንሳት የተጀመረው ላይ አሽከርካሪዎች በሰከነ፣በትግስት፣ በእርጋታ ማገልገል አለባችሁ ።
መልካም ቀን።

የተኛውም ዕጩ አሽከርካሪዎች ማሰልጠኛ ተቋም ለመመዝገብ ሲሄድ የወሰኝ ኩነት ሰርትፍኬት ማቅረብ አለበት። አቶ አገኘሁ ወርቁ።ሚዛን አማንበቅንጅት ያለመንጃ ፍቃድ የሚያሽከርክሩ በተላይ ባለሁለት...
08/02/2024

የተኛውም ዕጩ አሽከርካሪዎች ማሰልጠኛ ተቋም ለመመዝገብ ሲሄድ የወሰኝ ኩነት ሰርትፍኬት ማቅረብ አለበት። አቶ አገኘሁ ወርቁ።
ሚዛን አማን
በቅንጅት ያለመንጃ ፍቃድ የሚያሽከርክሩ በተላይ ባለሁለት ዕግር ተሽከርካሪዎች ጋር በተያያዘ በተደረገው ምልከታ በርካታ ወረዳዎች የውስጥ ቀበሌዎች አንዳንድ ያለዕድሜ(18 ዓመት በታች) የሆኑት ሞተር እያሽከረከሩ የታዩ ሲሆን መንጃ ፍቃድ እንደሌላቸው የተወሰኑ ከተያዙት የተረጋገጠ ሲሆን። የመንጃ ፍቃድ ሳይዙ የሚያሽከረክረው ቁጥጥር የሚጠናከር ሲሆን በምንም ምክንያት ወሳኝ ኩነት መረጃ ሳይዙ ወደ ስልጠና መግባት እንደማይችል እንደ ዞን ትራንስፖርት አቅጣጫ ተቀምጧል።
በዞናችን 6 የማሰልጠኛ ተቋም ሲኖር በምዝገባ ወቅት የወሳኝ ኩነት መረጃ እንዲያመጡ መደረግ አለበት። ይህ ተቋሙን ከተጠያቂነት የሚያድን ሲሆን ለትራፊክ እና ለመንገድ ደህንነት ለፀጥታ አካላት ለቁጥርም ይረዳል ተብሏል።

በሸኮ ወረዳ የመንገድ መሰረተ ልማት ተቀጣጥሎ በከተማ ውስጥለውስጥ፣ ጓን ለጓን ወደ ቀበሌን ከቀበሌ የሚያገናኘው ለዘመናት ያልታሰበ የመንገድ ከፈታ በህብረተሰቡ ተሳትፎ የተከፈተ ይገኛል። በጣ...
04/02/2024

በሸኮ ወረዳ የመንገድ መሰረተ ልማት ተቀጣጥሎ በከተማ ውስጥለውስጥ፣ ጓን ለጓን ወደ ቀበሌን ከቀበሌ የሚያገናኘው ለዘመናት ያልታሰበ የመንገድ ከፈታ በህብረተሰቡ ተሳትፎ የተከፈተ ይገኛል። በጣም የሚገርመው አንድ ቀበሌ እስከ 2 ሚሊዮን እያዋጣ አጠቃላይ ቀበሌዎች ወረፋ የተጠባበቁ ሲሆን ጀንጀቃ ላይ ስራ ላይ ነው።
👉 የተራራው ንጉስ ባለሰንሰላታሙ cat ማሽን እያገሳ ወደ ቡና በብዛት በሚመረትበት ግን መንገድ ብርቅ ወደሆነባት ጀንጀቃ ቀበሌ ወርዷል። ፈረሶች፣በቅሎች መናገር ቢችሉ ምን እንደሚሉ መገመት ቀላል ነው፣ የሰውን ትተን።
👉 ዋናው መንገድ መክፈት ብቻ ሳይሆን ወረዳው ጓን ለጓን ጠጠር ብቻ የሚያመርት ሽንጣሙ እስካቫተር ለተከፈቱት ለከተማ፣ለቀበሌ መንገዶች ጠጠር እያዘጋጀ ነው እስካሁን 37,000ሜትር ኪብ ደርሷል። ማሽኑ ይች ምንድናት ያለ ይመስላል ቀጥሎበታል።
👉በትላንትናው ቅዳሜ ሸኮ በነበርኩት በአየውት ክቡር አስተዳዳሪ አቶ አሪ እና ሉካኑ ወደ ጀንጀቃ ወርዶ ጓብኝቷል።
👉ከቅየሳ ጋር ተያይዞ የዞኑ ቀያሽ የሰርቨይር ዕቃዎቹን ጭኖ ወደ ጀንጀቃ ያቀናል። መልካም ዕለተ ዕሁድ።

Address

Mizan
Mizan Teferi

Opening Hours

Monday 02:30 - 06:30
07:30 - 11:30
Tuesday 02:30 - 06:30
07:30 - 11:30
Wednesday 02:30 - 06:30
07:30 - 11:30
Thursday 02:30 - 06:30
07:30 - 11:30
Friday 02:30 - 06:30
07:30 - 11:30

Telephone

+251478359046

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Bench Sheko Zone Transport and Road Dev't Department posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share