01/05/2026
የአዴት/ቴ/ሙ/ማ/ ኮሌጅ ስለ ስርአተ-ፆታ ስልጠና ሰጠ ።
ሚያዚያ 22/2018 ዓ.ም
አዴትቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጅ ለአስተዳደር ሰራተኞች እና አሰልጣኝ ኢንስትራክተሮች ስርአተ-ፆታን መሰረት ያደረገ የማስተማር ስነ-ዘዴ (GRP) Gender Responsiveness Pedagogy (GRP) ስልጠና በዘርፉ በሰለጠኑት በአቶ አዲሱ እምቢያለ እና ኢንስትራክተር ዙፋን አበበ አማካኝነት ስልጠናው ተሰቷል።
ይህ ስልጠና በFAWE (Forum of African Women Empowerment ) ድጋፍ አማካኝነት የተካሄደ ሲሆን ፦
ዋና ዓላማውም በኮሌጁ ውስጥ ባሉ ማንኛውም ስርዓተ - ፆታን በሚመለከቱ ጉዳዮች ላይ ማለትም በመማር ማስተማር እና በስልጠና ሂደቱ ውስጥ የስርአተ-ፆታ እኩልነትን እና ፍትሐዊ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ ነው ።
የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ ምኒችል ዓለም የስልጠናውን የመክፈቻ ንግግር በማድረግ ስለ ስልጠናው ይዘትና ቆይታ በመግለፅ የGRP ስልጠና መሠጠቱ ሰራተኞች ስለ ፆታ እና ስርአተ-ፆታ እኩልነት ያላቸውን ግንዛቤ በማሳደግ በኮሌጃችን ውስጥ ለሰልጣኝ ተማሪዎች ምቹ የሆነ የመማር ማስተማር አካባቢን ለመፍጠር ትልቅ ሚና እንዳለው ገልፀው የስርዓተ-ፆታ ማስፈፀሚያ መርሆችን በመከተል ስልጠናውን በተግባር እንድታውሉት የሚል የማሳሰቢያ መልክት አስተላልፈዋል ።
" እኩልነትና ፍትሐዊነት የሁላችንም ኃላፊነት ሊሆን ይገባል !!
/ የአዴት ቴ/ሙ/ማ/ ኮሌጅ
ህዝብ ግንኙነት /
ለበለጠ መረጃ ፦
http://www.https/t.Me/Adet
Telegram https://t.me/Adettc01