Adet Tvet College አዴት/ቴ/ሙ/ማ/ኮሌጅ

Adet Tvet College አዴት/ቴ/ሙ/ማ/ኮሌጅ Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Adet Tvet College አዴት/ቴ/ሙ/ማ/ኮሌጅ, Train station, near Tana College, Adet.

የአዴት/ቴ/ሙ/ማ/ ኮሌጅ  ስለ ስርአተ-ፆታ ስልጠና ሰጠ ።                           ሚያዚያ 22/2018 ዓ.ም   አዴትቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጅ  ለአስተዳደር ሰራተኞች ...
01/05/2026

የአዴት/ቴ/ሙ/ማ/ ኮሌጅ ስለ ስርአተ-ፆታ ስልጠና ሰጠ ።

ሚያዚያ 22/2018 ዓ.ም

አዴትቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጅ ለአስተዳደር ሰራተኞች እና አሰልጣኝ ኢንስትራክተሮች ስርአተ-ፆታን መሰረት ያደረገ የማስተማር ስነ-ዘዴ (GRP) Gender Responsiveness Pedagogy (GRP) ስልጠና በዘርፉ በሰለጠኑት በአቶ አዲሱ እምቢያለ እና ኢንስትራክተር ዙፋን አበበ አማካኝነት ስልጠናው ተሰቷል።

ይህ ስልጠና በFAWE (Forum of African Women Empowerment ) ድጋፍ አማካኝነት የተካሄደ ሲሆን ፦

ዋና ዓላማውም በኮሌጁ ውስጥ ባሉ ማንኛውም ስርዓተ - ፆታን በሚመለከቱ ጉዳዮች ላይ ማለትም በመማር ማስተማር እና በስልጠና ሂደቱ ውስጥ የስርአተ-ፆታ እኩልነትን እና ፍትሐዊ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ ነው ።

የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ ምኒችል ዓለም የስልጠናውን የመክፈቻ ንግግር በማድረግ ስለ ስልጠናው ይዘትና ቆይታ በመግለፅ የGRP ስልጠና መሠጠቱ ሰራተኞች ስለ ፆታ እና ስርአተ-ፆታ እኩልነት ያላቸውን ግንዛቤ በማሳደግ በኮሌጃችን ውስጥ ለሰልጣኝ ተማሪዎች ምቹ የሆነ የመማር ማስተማር አካባቢን ለመፍጠር ትልቅ ሚና እንዳለው ገልፀው የስርዓተ-ፆታ ማስፈፀሚያ መርሆችን በመከተል ስልጠናውን በተግባር እንድታውሉት የሚል የማሳሰቢያ መልክት አስተላልፈዋል ።


" እኩልነትና ፍትሐዊነት የሁላችንም ኃላፊነት ሊሆን ይገባል !!

/ የአዴት ቴ/ሙ/ማ/ ኮሌጅ
ህዝብ ግንኙነት /

ለበለጠ መረጃ ፦

http://www.https/t.Me/Adet
Telegram https://t.me/Adettc01

የአዴት/ቴ/ሙ/ማ/ ኮሌጅ  ሰልጣኞችን COC አስመዘነ ።             መጋቢት 22/2018 ዓ.ም      በሰሜን ጎጃም ዞን የአዴት/ቴ/ሙ/ማ/ ኮሌጅ  በተለያየ የሙያ ዘርፍ ማለትም ፦_...
31/03/2026

የአዴት/ቴ/ሙ/ማ/ ኮሌጅ ሰልጣኞችን COC አስመዘነ ።

መጋቢት 22/2018 ዓ.ም

በሰሜን ጎጃም ዞን የአዴት/ቴ/ሙ/ማ/ ኮሌጅ በተለያየ የሙያ ዘርፍ ማለትም ፦

_ በእንስሳት ድልብ 697
_ በወተት 105
_ በዶሮ እርባታ 36
_ በውጭ ሀገር የሥራ ሥምሪት 56
እና በመሳሰሉት የሙያ ስልጠና ሠልጣኞችን በማሰልጠን በቁጥር 894 የሚደርሱ ሰልጣኞችን COC እያስመዘነ ይገኛል ።

ከተመዛኞች መካከልም ዶሞስቲክ ወርክ/
የውጭ ሀገር የሥራ ሥምሪት ተመዛኞች ህገ- ወጥ የሰዎች ዝውውር የሚያስከትለውን ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳት እንዲሁም በዜጎች ላይ የሚደርሰውን አላስፈላጊ እንግልትና ጭቆና በመረዳት በአዲሱ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት መመሪያን በመከተል
በኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት (E-LMIS) ተመዝግበው የሰለጠኑ ተመዛኞች ናቸው ።

በሰሜን ጎጃም ዞን  በይ/ዴ/ወ/አስ/ ንግድና ገ/ልማት  እና ስራና ስልጠና ጽ/ቤት  አዘጋጅነት  በምግብ ስርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም/FS RP) በጀት ድጋፍ  የንግድ ኤግዚቪዥን  እና  ባዛ...
10/03/2026

በሰሜን ጎጃም ዞን በይ/ዴ/ወ/አስ/

ንግድና ገ/ልማት እና ስራና ስልጠና ጽ/

ቤት አዘጋጅነት በምግብ ስርዓት

ማጠናከሪያ ፕሮግራም/FS RP) በጀት

ድጋፍ የንግድ ኤግዚቪዥን እና ባዛር

ለተጠቃሚ ክፍት ተደረገ ።

የባዛሩ ዋና ዓላማም ፦

_ አምራች ድርጅቶች እና

ኢንተርፕራይዞች ምርታቸውን እና

አገልግሎታቸውን ያስተዋውቁበታል

_ የተለያዩ አካላት ልምድ

ይለዋወጡበታል

_ አዳዲስ ምርቶችን፣ አልባሳት፣

እቃወችን ፣ የምግብ ተዋጽኦ ፣

አትክልትና ፍራፍሬ የመሳሰሉትን

አምራቾች

በቀጥታ ከሸማች ማህበረሰቡ ጋር

በቀጥታ በልዩ ቅናሽ ይገበያዩበታል

እንዲሁም ሌሎችንም ጥቅሞች

ይኖረዋል ተብሎ የተዘጋጀ ሲሆን

የተለያዩ አምራች ድርጅቶች ምርት እና

አገልግሎታቸውን እንዲሁም

ቴክኖሎጃቸውን እያስተዋወቁ ይገኛሉ ።

ለአብነት ለመጥቀስ ያክልም ፦

የአዴት ቴ/ሙ/ማ/ኮሌጅ በኮሌጁ

አሰልጣኝ ሰራተኞች የተሰሩ የተለያዩ

ቴክኖሎጅ ማሽኖችን ያቀረበ ሲሆን

ከቀረቡት መካከል በትቂቱ
ለመጥቀስም ፦

_ ባለ 3 ፓትራ ኤሌክትሪካል

የዳቦ መጋገሪያ ማሽን

_ ባለ 6 ፓትራ ኤሌክትሪካል

የዳቦ ማንኳፈፊያ ማሽን

_ የላሜራ ቅርጽ ማውጫ ማሽን እና

ሌሎችም ይገኙበታል ።

( መጋቢት 01/2018 ዓ.ም
የአዴት ቴ/ሙ/ማ/ኮሌጅ ህ/ግ )

በአዴት/ቴ/ሙ/ማ/ ኮሌጅ  የውጭ ሐገር የስራ ስምሪት ሰልጣኞች  በስልጠና ላይ ።            የካቲት 20/2018 ዓ.ም     የአዴት/ቴ/ሙ/ማ/ ኮሌጅ  ከመደበኛው ስልጠና  በተጨማሪም...
27/02/2026

በአዴት/ቴ/ሙ/ማ/ ኮሌጅ የውጭ ሐገር የስራ ስምሪት ሰልጣኞች በስልጠና ላይ ።

የካቲት 20/2018 ዓ.ም

የአዴት/ቴ/ሙ/ማ/ ኮሌጅ ከመደበኛው ስልጠና በተጨማሪም የአጫጭር ሰልጣኞችን በመቀበል በተላያየ የሙያ ዘርፍ በንድፈ ሃሣብ እና በተግባር የተደገፈ ስልጠና እያሰለጠነ የሙያ ባለቤት እያደረገ ይገኛል ።

" ብቁና ተወዳዳሪ የሰለጠነ ዜጋ ማፍራት የዞትር ራዕይአችን ነው !!

የአዴት/ቴ/ሙ/ማ/ ኮሌጅ  የግቢ በር ግንባታ አስጀመረ ።            የካቲት 18/2018 ዓ.ም    የአዴት/ቴ/ሙ/ማ/ ኮሌጅ  በዋናው ግቢ  የግቢ በር ግንባታ ሥራ አስጀመረ ።    ...
25/02/2026

የአዴት/ቴ/ሙ/ማ/ ኮሌጅ የግቢ በር ግንባታ አስጀመረ ።

የካቲት 18/2018 ዓ.ም

የአዴት/ቴ/ሙ/ማ/ ኮሌጅ በዋናው ግቢ የግቢ በር ግንባታ ሥራ አስጀመረ ።
የግቢ በር ግንባታ ስራው ከ ቅዬሳ ፣ ፉትይንግ አውት እስከ መጨረሻ ሙሉ ሥራው በኮሌጁ አሰልጣኝ ኢንስትራክተሮችና ባለሙያዎች በእየ ሙያ ዘርፋቸው ግንባታ ሥራው እንደሚሰራም ተገልጿል ።

ለአፕ ግሬድ  እና  አዲስ ስልጠና ፈላጊዎች በሙሉ ፦
18/02/2026

ለአፕ ግሬድ እና አዲስ ስልጠና ፈላጊዎች በሙሉ ፦

የአዴት/ቴ/ሙ/ማ/ኮሌጅ ዲጅታል ላይቭራሪ ሕንፃ ግንባታ አስመረቀ ።      ጥር 18/2018 ዓ.ም     በሰሜን ጎጃም ዞን የአዴት ቴ/ሙ/ማ/ ኮሌጅ በይ/ዴ/ወ/አስ/ አልማ ጽ/ቤት አስተባባ...
26/01/2026

የአዴት/ቴ/ሙ/ማ/ኮሌጅ ዲጅታል ላይቭራሪ ሕንፃ ግንባታ አስመረቀ ።

ጥር 18/2018 ዓ.ም

በሰሜን ጎጃም ዞን የአዴት ቴ/ሙ/ማ/ ኮሌጅ በይ/ዴ/ወ/አስ/ አልማ ጽ/ቤት አስተባባሪነትና ድጋፍ የተሰራው ዲጅታል ላይቭራሪ ሕንፃ ግንባታ ስራውን አጠናቆ በማስመረቅ ለአገልግሎት ክፍት አደረገ ።

ዲጂታል ላይቨራሪው አገልግሎት መስጠት ሲጀምር የኮሌጁን ሰልጣኞችና ሰራተኞች ያለባቸዉን የንባብና የሪፈረንስ ችግር ከመቅረፉም ባሻገር ምቹ የስራ አካባቢን በመፍጠር ዲጅታል ኢትዮጵያን እውን በማድረግ የአገልግሎት አሰጣጥን በማሳለጥ ከዲጅታሉ ዓለም ጋር በመራመድ ኮሌጁን ከስልጠናም ባሻገር የቴክኖሎጅ ማዕከል የማድረግ ራዕይ ያለው ነው ተብሏል ።

በዚህ አጋጣሚም
የይ/ዴ/ወ/አስ፣ የአዴት ከተማ አስ፣ የአልማ ቅ/ጽ/ቤት ፣ አሰሪ ኮሚቴዎች፣ ህንፃተቋራጭ ሰራተኞች እና ሌሎችም ባለድርሻ አካላትና ተቋማት ላሳያችሁት ቁርጠኝነት የስራ ስምሪትና ክትትል ህንፃውን በአጭር ጊዜና በጥራት እንዲጠናቀቅ ስላደረጋችሁ ማመስገን እንወዳለን።

( የአዴት ቴ/ሙ/ማ/ኮሌጅ )

የአዴት ቴ/ሙ/ማ/ኮሌጅ የ6ወር ስራ አፈፃፀምን ገመገመ።              ጥር 14/2018 ዓ.ም የአዴት ቴ/ሙ/ማ/ኮሌጅ የ2018 በጀት ዓመት የ6ወር የስራ አፈፃፀም ሪፖርት ገመገመ።  ...
22/01/2026

የአዴት ቴ/ሙ/ማ/ኮሌጅ የ6ወር ስራ አፈፃፀምን ገመገመ።

ጥር 14/2018 ዓ.ም

የአዴት ቴ/ሙ/ማ/ኮሌጅ የ2018 በጀት ዓመት የ6ወር የስራ አፈፃፀም ሪፖርት ገመገመ።

ሪፖርቱን መነሻ በማድረግ በ6 ወራት ውስጥ የተከናወኑ ቁልፍ እና አባይት ተግባራትን በእየ ዘርፉ እና በእየ ቡድኑ የኮሌጁን ሆለንተናዊ የስራ እንቅስቃሴ በጥንካሬና በድክመት ተገምግሟል ፡፡

በጥንካሬ የታዩትን በመውሰድ ለቀጣይ 6ወራት ሁሉም በየድርሻው ከድክመቱ በመማር የተሻለ ተግባራትን ለመፈፀም ከወዲሁ አቅዶ መስራት ይጠበቃል በማለት የስራ አቅጣጫ ተቀምጦ ውይይቱ ተጠናቋል ።

እንኳን ለ2018 ዓ.ም ለጌታችንና ለመድሐኒታችን ለእየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያልን ፦          በዓሉ የሰላም፣ የጤና፣ የፍቅር፣ የደስታ፣ የመተሳሰብና የአብሮነ...
06/01/2026

እንኳን ለ2018 ዓ.ም ለጌታችንና ለመድሐኒታችን ለእየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያልን ፦

በዓሉ የሰላም፣ የጤና፣ የፍቅር፣ የደስታ፣ የመተሳሰብና የአብሮነት እንዲሆንልዎ መልካም ምኞቱን ይገልፃል !!

" መልካም የገና በዓል !!

ታህሳስ 28/2018 ዓ.ም ( የአዴት ቴ/ሙ/ማ/ኮሌጅ ህ/ግንኙነት)

የአዴት ቴ/ሙ/ማ/ኮሌጅ  ተጎበኘ ።     ታህሳስ 08/2018 ዓ.ም      በሰሜን ጎጃም ዞን የአዴት ቴ/ሙ/ማ/ኮሌጅ  የኮሌጁን ሁለንተናዊ  የስራ እንቅስቃሴ  እና አሁንዊ  የኮሌጁ ገፅታ...
17/12/2025

የአዴት ቴ/ሙ/ማ/ኮሌጅ ተጎበኘ ።

ታህሳስ 08/2018 ዓ.ም

በሰሜን ጎጃም ዞን የአዴት ቴ/ሙ/ማ/ኮሌጅ የኮሌጁን ሁለንተናዊ የስራ እንቅስቃሴ እና አሁንዊ የኮሌጁ ገፅታ ተጎበኘ ።

በመስክ ጉብኝቱም
የአማራ ክልል ስራና ክህሎት ም/ቢሮ ኃላፊዎች፣ የሰሜን ጎጃም ዞን ስራና ክህሎት መምሪያ ኃላፊ እና የአዴት ከተማ አስተዳደር ስራና ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፊ ፣ የይ/ዴ/ወ/አስተዳደር ስራና ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፊ እንዲሁም ሌሎች የአጋር ተቋማት ኃላፊዎች ም/ኃላፊዎች የኮሌጁን ሁለንተናዊ አሰራር እና የስራ እንቅስቃሴ ፣ የኮሌጁን ዲጅታል ላይበራሪ ፣ የመስሪያ ወርክ ሾፖችን ፣ ላቭ ክላሶችና የመማሪያ ክላሶችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል ።

(የአዴት ቴ/ሙ/ማ/ኮሌጅ ህ/ግ)

Address

Near Tana College
Adet

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Adet Tvet College አዴት/ቴ/ሙ/ማ/ኮሌጅ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Adet Tvet College አዴት/ቴ/ሙ/ማ/ኮሌጅ:

Share

Category