Adet Tvet College አዴት/ቴ/ሙ/ማ/ኮሌጅ

Adet Tvet College አዴት/ቴ/ሙ/ማ/ኮሌጅ Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Adet Tvet College አዴት/ቴ/ሙ/ማ/ኮሌጅ, Train station, near Tana College, Adet.

የአዴት ቴ/ሙ/ማ/ኮሌጅ  የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሥራን አከናወነ ።             ሐምሌ  23/2018 ዓ.ም በሰሜን ጎጃም ዞን በአዴት ከተማ አስተዳደር  የአዴት ቴ/ሙ/ማ/ኮሌ...
30/07/2026

የአዴት ቴ/ሙ/ማ/ኮሌጅ የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሥራን አከናወነ ።

ሐምሌ 23/2018 ዓ.ም

በሰሜን ጎጃም ዞን በአዴት ከተማ አስተዳደር የአዴት ቴ/ሙ/ማ/ኮሌጅ 3 የአረጋዊያን እና አቅመ ደካማ ቤት በማደስ የበጎነት ተግባራት ሥራን አከናወነ ።

ኮሌጁ 3ቱንም የአቅመ ደካሞች ቤት ከአዴት ከተማ አስተዳደር ሴቶች ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት ጋር በመነጋገር ተረክቦ ከ 55 ሽህ ብር በላይ ወጭ አውጥቶ በኮሌጁ ሙያተኞች እና ሰራተኞች ጉልበት ወጭ የተሸፈነው ይህ ሰብዓዊ ተግባር 3 ቱንም ቤቶች ሙሉ እድሳት አድርጎ ሰርቶ ያስረከበ ሲሆን

​ በዚህም የበጎነት ተግባር ላይ የኮሌጁ ዲንዎች እና ሠራተኞች በሥራው ላይ በመገኘት በሙያቸውና በጉልበታቸው ለበጎነት ተግባር በመስራታቸውና ላበረከቱት ሰብዓዊ ተግባር ደስተኞች መሆናቸውን በመግለፅ ይህ ማህበረሰብ ተኮር የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሥራ ለተቸገሩ ወገኖች ጋን በጠጠር ይደገፋል እንደሚባለው የማኅበረሰቡን የእርስ በርስ የመረዳዳትና የመደጋገፍ ባህልን እንደሚያጠናክርም ገልፀዋል ።

የአዴት ቴ/ሙ/ማ/ኮሌጅ  የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሥራን እያከናወነ ነው ።             ሐምሌ  22/2018 ዓ.ም በሰሜን ጎጃም ዞን በአዴት ከተማ አስተዳደር  የአዴት ቴ/ሙ/...
29/07/2026

የአዴት ቴ/ሙ/ማ/ኮሌጅ የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሥራን እያከናወነ ነው ።

ሐምሌ 22/2018 ዓ.ም

በሰሜን ጎጃም ዞን በአዴት ከተማ አስተዳደር የአዴት ቴ/ሙ/ማ/ኮሌጅ 3 የአረጋዊያን እና አቅመ ደካማ ቤት ከአዴት ከተማ አስተዳደር ከሚመለከተው ጽ/ቤት ጋር በመነጋገር ቤቶችን ተረክቦ ሙሉ ወጩን በመሸፈን አድሶ ሰርቶ ለማስረከብ ሥራውን ወስዶ በተቀናጀና በተደራጀ መንገድ በኮሌጁ ሰራተኞች እዬተከናወነ ይገኛል ።

የአዴት ቴ/ሙ/ማ/ኮሌጅ የስራ አፈፃፀም ግምገማ አደረገ።             ሐምሌ 09/2018 ዓ.ም የአዴት ቴ/ሙ/ማ/ኮሌጅ የ2018 በጀት ዓመት የ4ኛው ሩብ ዓመት የሥራ አፈፃፀም ግምገማ ...
16/07/2026

የአዴት ቴ/ሙ/ማ/ኮሌጅ የስራ አፈፃፀም ግምገማ አደረገ።

ሐምሌ 09/2018 ዓ.ም

የአዴት ቴ/ሙ/ማ/ኮሌጅ የ2018 በጀት ዓመት የ4ኛው ሩብ ዓመት የሥራ አፈፃፀም ግምገማ አደረገ።

በኮሌጁ በበጀት ዓመቱ የተከናወኑ
ተግባራት ከቁልፍ እና አባይት ተግባራት እንዲሁም የመልካም አስተዳደር ችግርን በውይይት ከመፍታት አንፃር በጥንካሬ እና በድክመት የተገመገመ ሲሆን

ከድክመቶች በመማር በጥንካሬ የታዩትን ተሞክሮ በመውሰድ ለቀጣይ ሥራ የተሻለ ለመፈፀም እራስን ከወዲሁ ማዘጋጀት እንደሚገባ በመግለፅ ለቀጣይ የክረምት ሥራዎችና ለ2019 በጀት ዓመት የሥራ አቅጣጫ በማስቀመጥ ውይይቱን በማጠናቀቅ

ከክረምት ሥራዎች አንዱ የሆነውን አረንጓዴ ችግኝ ተከላ በኮሌጁ ግቢ ውስጥ አረንጓዴ ውብና ማራኪ የሆነ ግቢና የሥራ ቦታ ለመፍጠረ የጫካ እና የውበት ችግኞችን ጠቅላላ ሰራተኛው በመትከል አሻራውን አስቀምጧል ።

የአዴት ቴ/ሙ/ማ/ኮሌጅ የውስጥ ጥራት ማረጋገጫ ስልጠና ተሰጠ ።       ግንቦት 27/2018 ዓ.ም  በአዴት ቴ/ሙ/ማ/ኮሌጅ  የውስጥ ጥራት ማረጋገጫና መመዘኛ  የሱፐርቪዥን እና ኢንስፔክሽ...
04/06/2026

የአዴት ቴ/ሙ/ማ/ኮሌጅ የውስጥ ጥራት ማረጋገጫ ስልጠና ተሰጠ ።

ግንቦት 27/2018 ዓ.ም

በአዴት ቴ/ሙ/ማ/ኮሌጅ የውስጥ ጥራት ማረጋገጫና መመዘኛ የሱፐርቪዥን እና ኢንስፔክሽን ክትትልና ቁጥጥር ግምገማ የኮሌጁን ሆለንተናዊ የስራ እንቅስቃሴ እና የትምህርት ጥራት ለማረጋገጥ ስላለው ጠቀሜታ ለጠቅላላ ሰራተኛው ስልጠና ተሰጠ ።

03/06/2026
የአዴት/ቴ/ሙ/ማ/ ኮሌጅ  ስለ ስርአተ-ፆታ ስልጠና ሰጠ ።                           ሚያዚያ 22/2018 ዓ.ም   አዴትቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጅ  ለአስተዳደር ሰራተኞች ...
01/05/2026

የአዴት/ቴ/ሙ/ማ/ ኮሌጅ ስለ ስርአተ-ፆታ ስልጠና ሰጠ ።

ሚያዚያ 22/2018 ዓ.ም

አዴትቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጅ ለአስተዳደር ሰራተኞች እና አሰልጣኝ ኢንስትራክተሮች ስርአተ-ፆታን መሰረት ያደረገ የማስተማር ስነ-ዘዴ (GRP) Gender Responsiveness Pedagogy (GRP) ስልጠና በዘርፉ በሰለጠኑት በአቶ አዲሱ እምቢያለ እና ኢንስትራክተር ዙፋን አበበ አማካኝነት ስልጠናው ተሰቷል።

ይህ ስልጠና በFAWE (Forum of African Women Empowerment ) ድጋፍ አማካኝነት የተካሄደ ሲሆን ፦

ዋና ዓላማውም በኮሌጁ ውስጥ ባሉ ማንኛውም ስርዓተ - ፆታን በሚመለከቱ ጉዳዮች ላይ ማለትም በመማር ማስተማር እና በስልጠና ሂደቱ ውስጥ የስርአተ-ፆታ እኩልነትን እና ፍትሐዊ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ ነው ።

የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ ምኒችል ዓለም የስልጠናውን የመክፈቻ ንግግር በማድረግ ስለ ስልጠናው ይዘትና ቆይታ በመግለፅ የGRP ስልጠና መሠጠቱ ሰራተኞች ስለ ፆታ እና ስርአተ-ፆታ እኩልነት ያላቸውን ግንዛቤ በማሳደግ በኮሌጃችን ውስጥ ለሰልጣኝ ተማሪዎች ምቹ የሆነ የመማር ማስተማር አካባቢን ለመፍጠር ትልቅ ሚና እንዳለው ገልፀው የስርዓተ-ፆታ ማስፈፀሚያ መርሆችን በመከተል ስልጠናውን በተግባር እንድታውሉት የሚል የማሳሰቢያ መልክት አስተላልፈዋል ።


" እኩልነትና ፍትሐዊነት የሁላችንም ኃላፊነት ሊሆን ይገባል !!

/ የአዴት ቴ/ሙ/ማ/ ኮሌጅ
ህዝብ ግንኙነት /

ለበለጠ መረጃ ፦

http://www.https/t.Me/Adet
Telegram https://t.me/Adettc01

የአዴት/ቴ/ሙ/ማ/ ኮሌጅ  ሰልጣኞችን COC አስመዘነ ።             መጋቢት 22/2018 ዓ.ም      በሰሜን ጎጃም ዞን የአዴት/ቴ/ሙ/ማ/ ኮሌጅ  በተለያየ የሙያ ዘርፍ ማለትም ፦_...
31/03/2026

የአዴት/ቴ/ሙ/ማ/ ኮሌጅ ሰልጣኞችን COC አስመዘነ ።

መጋቢት 22/2018 ዓ.ም

በሰሜን ጎጃም ዞን የአዴት/ቴ/ሙ/ማ/ ኮሌጅ በተለያየ የሙያ ዘርፍ ማለትም ፦

_ በእንስሳት ድልብ 697
_ በወተት 105
_ በዶሮ እርባታ 36
_ በውጭ ሀገር የሥራ ሥምሪት 56
እና በመሳሰሉት የሙያ ስልጠና ሠልጣኞችን በማሰልጠን በቁጥር 894 የሚደርሱ ሰልጣኞችን COC እያስመዘነ ይገኛል ።

ከተመዛኞች መካከልም ዶሞስቲክ ወርክ/
የውጭ ሀገር የሥራ ሥምሪት ተመዛኞች ህገ- ወጥ የሰዎች ዝውውር የሚያስከትለውን ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳት እንዲሁም በዜጎች ላይ የሚደርሰውን አላስፈላጊ እንግልትና ጭቆና በመረዳት በአዲሱ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት መመሪያን በመከተል
በኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት (E-LMIS) ተመዝግበው የሰለጠኑ ተመዛኞች ናቸው ።

በሰሜን ጎጃም ዞን  በይ/ዴ/ወ/አስ/ ንግድና ገ/ልማት  እና ስራና ስልጠና ጽ/ቤት  አዘጋጅነት  በምግብ ስርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም/FS RP) በጀት ድጋፍ  የንግድ ኤግዚቪዥን  እና  ባዛ...
10/03/2026

በሰሜን ጎጃም ዞን በይ/ዴ/ወ/አስ/

ንግድና ገ/ልማት እና ስራና ስልጠና ጽ/

ቤት አዘጋጅነት በምግብ ስርዓት

ማጠናከሪያ ፕሮግራም/FS RP) በጀት

ድጋፍ የንግድ ኤግዚቪዥን እና ባዛር

ለተጠቃሚ ክፍት ተደረገ ።

የባዛሩ ዋና ዓላማም ፦

_ አምራች ድርጅቶች እና

ኢንተርፕራይዞች ምርታቸውን እና

አገልግሎታቸውን ያስተዋውቁበታል

_ የተለያዩ አካላት ልምድ

ይለዋወጡበታል

_ አዳዲስ ምርቶችን፣ አልባሳት፣

እቃወችን ፣ የምግብ ተዋጽኦ ፣

አትክልትና ፍራፍሬ የመሳሰሉትን

አምራቾች

በቀጥታ ከሸማች ማህበረሰቡ ጋር

በቀጥታ በልዩ ቅናሽ ይገበያዩበታል

እንዲሁም ሌሎችንም ጥቅሞች

ይኖረዋል ተብሎ የተዘጋጀ ሲሆን

የተለያዩ አምራች ድርጅቶች ምርት እና

አገልግሎታቸውን እንዲሁም

ቴክኖሎጃቸውን እያስተዋወቁ ይገኛሉ ።

ለአብነት ለመጥቀስ ያክልም ፦

የአዴት ቴ/ሙ/ማ/ኮሌጅ በኮሌጁ

አሰልጣኝ ሰራተኞች የተሰሩ የተለያዩ

ቴክኖሎጅ ማሽኖችን ያቀረበ ሲሆን

ከቀረቡት መካከል በትቂቱ
ለመጥቀስም ፦

_ ባለ 3 ፓትራ ኤሌክትሪካል

የዳቦ መጋገሪያ ማሽን

_ ባለ 6 ፓትራ ኤሌክትሪካል

የዳቦ ማንኳፈፊያ ማሽን

_ የላሜራ ቅርጽ ማውጫ ማሽን እና

ሌሎችም ይገኙበታል ።

( መጋቢት 01/2018 ዓ.ም
የአዴት ቴ/ሙ/ማ/ኮሌጅ ህ/ግ )

Address

Near Tana College
Adet

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Adet Tvet College አዴት/ቴ/ሙ/ማ/ኮሌጅ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Adet Tvet College አዴት/ቴ/ሙ/ማ/ኮሌጅ:

Shortcuts

Share

Category