የፅዮን ማርያም ልጅ

የፅዮን ማርያም ልጅ Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from የፅዮን ማርያም ልጅ, Travel Service, addis ababa, Addis Ababa.

ተወገድ ከፊቴ ተፈታታኝ ሁሉይረዳኛል ይረዳኛል ጊዮርጊስ ኃያሉ    የልዳው ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ     ለፈለጉት ለወደደዱት  ፈጥሮ ነው የሚደርስነፍሴ አትጨነቂ ጽኚ በእምነትአይተውሽም ፍጡነ...
29/08/2021

ተወገድ ከፊቴ ተፈታታኝ ሁሉ
ይረዳኛል ይረዳኛል ጊዮርጊስ ኃያሉ
የልዳው ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ
ለፈለጉት ለወደደዱት ፈጥሮ ነው የሚደርስ
ነፍሴ አትጨነቂ ጽኚ በእምነት
አይተውሽም ፍጡነ ረድኤት
ሊወጠኝ ያገሳል የዚህ ዓለም አውሬ
ድረስልኝ ቅዱስ ጊዮርጊሰ ቋሚ ምስክሬ
በመተከዜን ልተው ልጽናና በመንፈስ
ይረዳኛል ይረዳኛል ሰማዕቱ ጊዮርጊስ

  ገብርኤል ሀያል መልአከ ሰላም መልአከ ብሥራትየምታወጣ የእግዚያብሔርን ልጅ ከሚነድ እሳትፍቅርህ ተስሏል በልባችንፊትህ ቆመናል ባርከን ብለን/2/የጽናታቸው ዝና ሲሰማከዛች ባቢሎን ከሞት ከተ...
25/08/2021



ገብርኤል ሀያል መልአከ ሰላም መልአከ ብሥራት
የምታወጣ የእግዚያብሔርን ልጅ ከሚነድ እሳት
ፍቅርህ ተስሏል በልባችን
ፊትህ ቆመናል ባርከን ብለን/2/

የጽናታቸው ዝና ሲሰማ
ከዛች ባቢሎን ከሞት ከተማ
ህጻናት ሳሉ በራ እምነታቸው
ቆመህ ተገኘህ መሀከላቸው

ውሀው ሲዘልል ቢያስደነግጥም
በጋኖቹ ውስጥ ቢነዋወጥም
ጸንተው ዘመሩ ልጅና እናቱ
አንተ ስትደርስ ከዛ ከእሳቱ

ቂርቆስም ጸና ሞትን ሳይፈራ
አንተ ስላለህ ከእነሱ ጋራ
አትፍሪ አላት ስለምን ትፍራ
አምነው ድል ነሱት ያንን መከራ

እኔም አማናለሁ አድነኝ ብዬ
ቆመህ አማልደኝ ከቸር ጌታዬ
ክፉውን ዘመን የማልፍበትን
ጽናትን ስጠኝ ድል ልንሳበትን

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ

ሀገራችን ውብ ድንቅ ማራኪ ተፈጥሮ መልካምድሯ የሚያስደምም ሌሎች የሚመኟት መሆኑን በግልፅ እያየነው ነው እኛ ግን በገዛ ቤታችን ሠላማችን እያጣን እየተባላን እየተገዳደልን በጦርነት ለመጠፋፋት...
23/08/2021

ሀገራችን ውብ ድንቅ ማራኪ ተፈጥሮ መልካምድሯ የሚያስደምም ሌሎች የሚመኟት መሆኑን በግልፅ እያየነው ነው እኛ ግን በገዛ ቤታችን ሠላማችን እያጣን እየተባላን እየተገዳደልን በጦርነት ለመጠፋፋትና የምንወዳትን ሀገራችንን ለጠላት ሀገራት ልናስረክብ ተቻኩለናል የሠላም ምንነት አልገባንም እንዲገባን ግን የሌሎች በጦርነት የጠፉ ሀገራትን ተመልክተን እንማር ።

ሰሚነሽ ኪዳነ ምህረት እንጦጦ ኪዳነ ምህረት
22/08/2021

ሰሚነሽ ኪዳነ ምህረት
እንጦጦ ኪዳነ ምህረት

ኢትዮጵያ ሠላምሽ ይብዛ 💚💛❤️:ያሳደከኝ አባቴ ሰማዕቱ ጊዮርጊስ እምዬን ኢትዮጵያን አብዝተክ ጠብቅልኝ ሠላሟንም መልስልን።
17/08/2021

ኢትዮጵያ ሠላምሽ ይብዛ 💚💛❤️:

ያሳደከኝ አባቴ ሰማዕቱ ጊዮርጊስ እምዬን ኢትዮጵያን አብዝተክ ጠብቅልኝ ሠላሟንም መልስልን።

ኢትዮጵያ ሠላምሽ ይብዛ 💚💛❤️አላዛር ኢትዮጵያ ከመቃብር ውጪመግነዝሽ ይፈታ ከጠላት አምልጪትንሳኤሽ ይሆናል እንቅልፍሽ አብቅቶንጉስሽ ለአጥፊው አይተውሽም ከቶ----‑----------------...
14/08/2021

ኢትዮጵያ ሠላምሽ ይብዛ 💚💛❤️

አላዛር ኢትዮጵያ ከመቃብር ውጪ
መግነዝሽ ይፈታ ከጠላት አምልጪ
ትንሳኤሽ ይሆናል እንቅልፍሽ አብቅቶ
ንጉስሽ ለአጥፊው አይተውሽም ከቶ
----‑-------------------
ባደረብሽ ህመም ሞተሽ አናይሽም
ኢትዮጵያ ስለአንቺ ከቶ ዝም አንልም
ወደ ፈጣሪያችን ወደአንቺ ፈጣሪ
እንፀልያለን ኢትዮጵያ እንድትኖሪ

ኢትዮጵያ  💚💛❤️ያደረብሽ ህመም ለሞት አይሰጥሽምትንሳኤሽን እንጂ ሞትሽን አናይምእግዚአብሔር ያኑርሽ ክፋትን አሻግሮጥፋትሽን የሚመኝ ይታይ አቀርቅሮ 💚💛❤️          💚💛❤️ሠማይሽ ቢጠቁ...
13/08/2021

ኢትዮጵያ 💚💛❤️

ያደረብሽ ህመም ለሞት አይሰጥሽም
ትንሳኤሽን እንጂ ሞትሽን አናይም
እግዚአብሔር ያኑርሽ ክፋትን አሻግሮ
ጥፋትሽን የሚመኝ ይታይ አቀርቅሮ
💚💛❤️ 💚💛❤️
ሠማይሽ ቢጠቁርም ፀሐይ አዝቅዝቃ
ንጋት ይወርስሻል እግዚአብሔር ሲል በቃ
እየተገዳደልን አለን ተጨካክነን
ተፈፀመ በለን ይሄን የጭንቅ ዘመን

እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ (ለምን እንላለን?••••••--------------------"ምስጢሩ"---------------------በቤተ ክርስቲያናችን ስርዓት ሁል ጊዜ ካህኑ እግዚአብሔርከታሰራች...
11/08/2021

እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ (ለምን እንላለን?••••••

--------------------"ምስጢሩ"---------------------

በቤተ ክርስቲያናችን ስርዓት ሁል ጊዜ ካህኑ እግዚአብሔር
ከታሰራችሁበት ኃጥያት ማስሪያ ይፍታችሁ ሲሉ 12ጊዜ
እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስና 12ጊዜ ደግሞ በእንተ እግዚእተነ
ማርያም መሐረነ ክርስቶስ ያስብላሉ። ካህናት ና ምእመናን
በጣቶቻችን እየቆጠርን ይህንኑ 12ጊዜ እንላለን።
እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ ማለት አቤቱ ክርስቶስ ማረን ሲሆን
በእንተ እግዚእተነ ማርያም መሐረነ ክርስቶስ ደግሞ ስለ እመቤታችን ማርያም ብለህ ክርስቶስ ሆይ ማረን ማለት ነው።
አስራ ሁለት ጊዜ መሐረነ መባሉ ለቀኑ 12 ሰዓት በእንነ
እግዚእተነ ማርያም ደግሞ ለሊቱን 12 ሰዓት ሲሆን
በአጠቃላይ በየሰዓቱ ለሰራነው ኃጥያት በሃይ አራቱ ፣24ቱ
ሰዓት ምሕረት እናገኝ ዘንድ ነው።
ሌላው አስራ ሁለት ጊዜ የሆነበት ምክንያት÷
1ኛው በስመ ሥላሴ ነው እያንዳንዱ ፊደል
አ ብ ወ ል ድ መ ን ፈ ስ ቅ ዱ ስ
፩ ፪ ፫ ፬ ፭ ፮ ፯ ፰ ፱ ፲ ፲፩ ፲፪

2ኛው ይድህነታችን ምክንያት በሆነች በእመቤታችን ስም ፊደል ነው።
ቅ ድ ስ ት ድ ን ግ ል ማ ር ያ ም
፩ ፪ ፫ ፬ ፭ ፮ ፯ ፰ ፱ ፲ ፲፩ ፲፪

---------------- "እግዚኦ "------------------

አቆጣጠረም እግዚኦ መሐረነ ሲባል በአውራ ጣት አይቆጠሩ
ከጠቋሚ ጣት ወድ ታች ፣ ቀጥሎ በመሐል ጣት ወደ ላይ
ከዚያም በቀለበት ጣት ወደ ታች ተደርጎ በማር ያም ጣት/
በትንሿ/ ጣት ወደ ላይ ነው።
ከጠቋሚ ጣት ወደ ታች ~አምላካችን እየሱስ ክርስቶስ እኛን ለማዳን ከሰማይ ሰማያት መውረዱን በዚህ ምድር መመላለሱን ሕማሙንና ሞቱን እናስባለን።
በመሐል ጣት ወደ ላይ ~ማረጉን ወደ ስማይ መውጣቱን
በቀለበት ጣት ወደ ታች ስንቆጥር ወደዚች አለም ለፍርድ መምጣቱን፣ በትንሿ/ጣት ወደ ላይ ስንወጣ ደግሞ በትንሳኤ ዘጉባኤ ይዞን ወደ ሰማይ እንደሚያወጣን እያሰብን ነው።

--------------------- "በእንተ "------------------

በእንተ እግዚተነ ማርያም ስንል አቆጣጠሩ ከትንሿ ጣት ወደ
ታች ይጀመርና በጠቋሚ ጣት ወደ ላይ ይፈጸማል ይህም
እመቤታችን ድንግል ማርያም ከትሕትና ወደ ልዕልና ከፍ ማለቷን የሚያሳይ ምስጢር ነው።

በእንተ ሲባል በትንሿ ጣት ወደ ታች ይጀመራል እራሷን ዝቅ አድርጋ የትህትናዋ ምሳሌ ስለሆነ ነው ከላይ ወደ ታች ሚጀመረው።

" ራሱን ከፍ የሚያደርግ ሁሉ ይዋረዳል፣ ራሱንም የሚያዋርድ ሁሉ ከፍ ይላል"፣የማት ወን 23፣12

ደግሞ የበእንት ፍጻሜ ወደላይ የሚያልቀው ሚስጢሩ እመቤታችን በሙቃብር አልቆየችም ወደ ላይ አረገች ማለት ነው።

"አቤቱ፣ ወደ ዕረፍትህ ተነሥ፣ አንተና የመቅደስህ ታቦት"
መዝ 132:8

ስንዱዋ እመቤት ቅድስት ቤተክርስቲያን ማንኛውንም ነገር
ያለ ትርጉም አታደርግም።
የአባቶቻችን በርከት ይደርብን። #አሜን፫

የተናገሩት ሁሉ እየተፈፀመ ነው
10/08/2021

የተናገሩት ሁሉ እየተፈፀመ ነው

Address

Addis Ababa
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የፅዮን ማርያም ልጅ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category