24/12/2024
እንኳን አደረሳችሁ
ለቅዱስ ገብርኤል አመታዊ ክብረ በዓል ወደ ሐዋሳ መሔድ ለምትፈልጉ የበዓሉ ተሳታፊዎች በሙሉ ፐብሊክ ሰርቪስ ትራንስፖርት አገልግሎት መነሻውን አዲስ አበባ በማድረግ ወደ ሐዋሳ የጉዞ አገልግሎት እንደሚሰጥ ለማስታወስ እንወዳለን።
ለረጅም ጊዜያት በማሽከርከር ብቃታቸውን ባስመሰከሩ ባስ ካፒቴኖቻችን በአገር አቋራጭ ባሶች ደህንነተዎ ተጠብቆ ካሰቡት ይደርሳሉ::
የፐብሊክ ሰርቪስ ትራንስፖርት አገልግሎት አገር አቋራጭ አውቶቢሶች ከመቀመጫቸው ምቾት በተጨማሪ አካል ጉዳተኞች ወደባሱ የሚሳፈሩበት አሳንሰር (ሊፍት) ፣ የስልክ ቻርጀር ማድረጊያዎች ፣ ዋይፋይ እና መፀዳጃ የተገጠመላቸው መሆኑ ልዩ ያደርጋቸዋል::
ትኬት ባሉበት ሆነው ወደ ነፃ የጥሪ ማዕከላችን 9439 በመደወል በቴሌብር ፣ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና በሁሉም የግል ባንኮች ትኬቶችን ማግኝት የሚችሉ ሲሆን በተጨማሪ የትኬት ቢሮዎቻችን ላምበረት ፣ ቃሊቲ ፣ አየር ጤና እና አስኮ ትኬቶችን ማግኘት ይችላሉ::
ለተጨማሪ መረጃ 9439 ላይ ይደውሉ::