10/12/2025
ደብዳቤ ቁ፡ 01-1-34/1432
ሕዳር 30 ቀን 2018 ዓ.ም
ጉዳዩ፡-የገቢ ምርቶች የኢትዮጵያ ደረጃ አተገባበርን ይመለከታል
. . ከዚህ ቀደም ሲተገበር የነበረው የVOC አሰራር የስምምነት ጊዜው በመጠናቀቁ የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት አለም አቀፍ ጨረታ በማውጣት ከተመረጡት Bureau Veritas TUV Rheinland Middle East FZE: COTECNA Inspection SA World Standardization Certification & Testing Group ከተባሉ አራት አለም አቀፍ የተስማሚነት ምዘና አካላት ጋር ስምምነት በማድረግ በ13 ምርቶች ላይ ከየምርቶቹ መነሻ ሀገር የምርቶቹን ጥራት በPVOC የአሰራር ስርአት ቁጥጥር እንዲደረግ እንዲሁም የተቀሩት 17 ምርቶች ሀገር ውስጥ ከገቡ በኃላ ድርጅቱ የVerification of Conformity ስራ እንደሚያከናውን ስደቁ 4/1/61/68/18 በቀን 24/03/2018 ዓ.ም በተጻፈ ደብዳቤ እንዳሳወቃቸው ገልጸው፡፡
በሀገር ውስጥ አቅም የላብራቶሪ ፍተሻ ማድረግ የማይቻሉ በአባሪው የተገለጹትን የተመረጡ ከዉጪ ወደ ሀገር ዉስጥ የሚገቡትን 13 ምርቶችን ከመነሻ ሀገራት በPVOC አሰራር ጥራታቸዉ ተረጋግጦ እንዲላኩ ማድረግ እንዲቻል እና ፕሮግራሙ እንዲቀጥል እንዲደረግ እንዲሁም የተቀሩት 17 ምርቶች ሀገር ውስጥ ከደረሱ ቡኃላ በኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት አስፈላጊውን የVerification of Conformity ስራ በማከናወን ጥራታቸውን የማረጋገጥ ስራ የሚያከናውን ስለሆነ ለሁሉም ባንኮች መመሪያው እንዲተላለፍ አስፈላጊዉን ትብብር እንዲደረግ ጠይቀው የጉምሩክ ኮሚሽንም የጉምሩክ ሥነ-ስርዓት በሚያከናዉንባቸዉ ቅ/ጽ/ቤቶች እነዚህ ምርቶች የኢትዮጵያ ደረጃዎች ተፈጻሚነት አስፈላጊዉን ትብብር እንዲያደርግ በማሳወቅ ከዚህ ቀደም የPVOC የአሠራር ሥርዓት ሲተገበርባቸው የነበሩ ምርቶች አባሪ ተደርገው በተያያዙት ምርቶች የተተኩ መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር በደብዳቤ ቁጥር 01-1-34/1432 ሕዳር 30/2018 ዓ.ም በፃፈው ደብዳቤ ለብሔራዊ ባንክ እንዲሁም በግልባጭ ለጉምሩክ ኮምሽን እና ለባለድርሻ አካላት ገልፆል፡፡
pdf. ተያይዟል📎🤳 https://t.me/sirius_logistics/213
ለፈጣን መረጃዎች፦
Telegram 👇👇
https://t.me/sirius_logistics
https://t.me/sirius_logistics
https://t.me/sirius_logistics