25/02/2026
ቲሸርት። ፒዛ። 45 ደቂቃዎች… እና ዓለም ያላየው ሰብአዊነት።
እሷ በተከለከለ ቦታ ተቀምጣ ነበር።
ህጉ ግልጽ ነበር — እዚህ ቦታ መቀመጥ አትችልም።
ኦፊሰር ሚካኤል ሪቨርስ መኪናውን አቆመ።
ሊያባርራት መጣ።
ይህ ሥራው ነበር።
እሷ ምንም አልተናገረችም።
ብቻ ተቀምጣ ነበር።
ከዚያ ዓይኑን በቲሸርቷ ላይ አደረገ።
“ቤት አልባ።
ማንም የማያየኝ ሞት ንቆ የተወኝ።” ይላል
ያነበበው ፁሁፍ ለፖሊሱ ቀላል አልነበር።
ግን ልቡን መታው።
አንድ እርምጃ ወደ ኋላ ተመለሰ።
“ስምሽ ማን ነው?” ብሎ ጠየቀ።
“ሚሼል…” አለች በቀስታ።
ያ ቀን ህጉን ሊያስፈጽም መጣ።
ግን ሰብአዊነትን መረጠ።
ከጥቂት ደቂቃ በኋላ ተመለሰ — በእጁ ፒዛ ነበር።
ከጎኗ በሣር ላይ ተቀመጠ።
አይደለም 5 ደቂቃ።
አይደለም 10 ደቂቃ።
45 ደቂቃዎች።
ስለ ልጆቿ ነገረችው —
በጉበት በሽታ ምክንያት ከሞተች 3ቀን ያለፋት
የ23 ዓመት አመት ሴት ልጅ እንደነበራት
አሁን ሁሉ ነገሯ እንደጨለመባት ምግብ ከበላች 3ቀን እንዳለፋት ነገረችው።
ፖሊሱም ባለው አቅም ፒዛ እና ለስላሳ ገዛላት
በዚያ ቀን ፒዛ ብቻ አልተሰጣትም…
ክብር ተሰጣት።
መታየት ተሰጣት።
ሰው መሆኗ ተመለሰ።
አንድ እንግዳ ፎቶ አነሳ።
ፎቶው በሺዎች ተጋራ።
ሰዎች “ጀግና!” አሉ።
ግን ለ ፖሊሱ ያ ቀን ስለ ፎቶ አልነበረም።
ስለ አንዲት ሴት —
ዓለም ያላየችውን ሴት —
ማየት ነበር።
አንዳንድ ጊዜ ጀግና መሆን
ሰውን መቆጣጠር አይደለም…
ልብን መክፈት ነው።🙏🙏🙏🙏