Aseb/አሰብ

Aseb/አሰብ Assab is a port city. አሰብ የኢትዮጵያ የወደብ ከተማ ስትሆን። ኢትዮጵያ ከለላው ዓለም ለመገናኘት ማንኛውንም ነገር ከውጭ ለማስገባት የምትጠቀምበት በር ናት።

01/04/2026
30/03/2026

ከመገለል ወደ ማዕከልነት፡ የመጋቢት ለውጥ እና የኢትዮጵያ ፖለቲካዊ አካታችነት አዲስ ምዕራፍ
*****************************

የመጋቢት 2010 ዓ.ም ለውጥ በኢትዮጵያ ዘመናዊ የፖለቲካ ታሪክ ውስጥ ቀደም ሲል የነበረውን የተገደበ እና የተወሰኑ ቡድኖች ብቻ የበላይ የሆኑበትን ሥርዓት በመቀየር ረገድ ትልቅ የታሪክ ምዕራፍ ሆኖ ይመዘገባል።

ይህ ለውጥ በተለይ ላለፉት ሦስት አሥርተ ዓመታት "አጋር" በሚል መጠሪያ ከማዕከላዊ የውሳኔ ሰጪነት ሚና ተገልለው የነበሩ የኅብረተሰብ ክፍሎችን ወደ መሐል ያመጣበት ሂደት ዋና መገለጫው ነው።

ቀደም ሲል በነበረው የኢሕአዴግ አወቃቀር ውስጥ አራቱ አባል ድርጅቶች ብቻ የሀገራችንን ዕጣ ፈንታ የሚወስኑበት ሲሆን ፤ እንደ ሶማሌ፣ አፋር፣ ቤንሻንጉል-ጉሙዝ፣ ጋምቤላ እና ሐረሪ ያሉ ክልሎች በሞግዚትነት የሚመሩበት ሥርዓት ሰፍኖ ቆይቷል።

ይህ አሠራር በክልሎቹ ሕዝቦች ዘንድ የሁለተኛ ዜግነት ስሜት በመፍጠር ለሀገራዊ አንድነት መላላት ምክንያት ሆኖ የቆየ ቢሆንም፣ ከለውጡ ማግስት ይህ ታሪካዊ አድልዎ በውህደት ተቀይሯል።

የቀድሞ "አጋር" ክልል ተወካዮች በከፍተኛ የሥልጣን እርከን ማለትም በሥራ አስፈፃሚ እና በማዕከላዊ ኮሚቴ ውስጥ እኩል ውክልና እንዲኖራቸው በማድረግ የክልሎችን እኩልነት በተግባር ተረጋግጧል።

ከዚህም ጎን ለጎን በስደት የነበሩ የፖለቲካ ኃይሎች ወደ ሀገር ቤት ገብተው በሰላማዊ መንገድ እንዲታገሉ መደረጉ ለአንድ ፓርቲ የበላይነት ስርዓት ማብቃት ትልቅ መሠረት ጥሏል።

ምንም እንኳ የፖለቲካ ባህላችንን ከእልህ ወደ ውይይት የመቀየር ጉዞ አሁንም ፈተናዎች ቢገጥሙትም፣ የመጋቢት ለውጥ ያስገኘው ፖለቲካዊ አካታችነት ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ታሪካዊ መነሻ ነው።

ይህንን ዕድል ለዘላቂ ሰላም ማዋል የሁሉም ፖለቲካዊ ተዋናዮች የጋራ ኃላፊነት መሆኑን መገንዘብ ይገባል።

በለሚ ታደሰ

ሙሉ መረጃውን በአስተያየት መስጫው ያገኙታል! 🔗

Join my page
30/03/2026

Join my page

ኢትዮጵያ ለአለም ንግድ ድርጅት አባልነት የመጨረሻው መስመር ላይ መድረሷ ተገለፀ
29/03/2026

ኢትዮጵያ ለአለም ንግድ ድርጅት አባልነት የመጨረሻው መስመር ላይ መድረሷ ተገለፀ

ኢትዮጵያ ለዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት የመጨረሻው መስመር ላይ መድረሷ ተገለጸ

: ለዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ድርድር ላይ የቆየችው ኢትዮጵያ የመጨረሻው መስመር ላይ መድረሷ ተገለጸ፡፡
በንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትሩ ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) የሚመራው የኢትዮጵያ ልዑክ ለካሜሩን ያውንዴ እየተካሄደ ባለው 14ኛው የዓለም ንግድ ድርጅት የሚኒስትሮች ኮንፍረንስ እየተሳተፈ ነው፡፡
የልዑክ ቡድኑ አባል ከሆኑት መካከል የብሔራዊ ባንክ ገዥ ኢዮብ ተካልኝ የዓለም የንግድ ድርጅትን ጠቅሰው በጻፉት ጽሑፍ፣ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባልነትን ለመቀላቀል የመጨረሻ መስመር ላይ ነች ብለዋል፡፡
መጋቢት 17 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ ለአራት ተከታታይ ቀናት በሚቆየው ኮንፈረንስ፣ የኢትዮጵያ ተደራዳሪ ቡድን ከድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ጋር ተገናኝቶ መምክሩን ከቦታው የወጣው መረጃ ያመላክታል፡፡
ከ22 አገሮች ጋር የድርጅቱ አባል ለመሆን ድርድር እያካሄዱ ከሚገኙት አገሮች መካከል ኢትዮጵያ አባልነቱን ለመቀላቀል ጥረት ከጀመረች ሁለት አሥር ዓመታት አልፈዋታል፡፡
የድርጅቱ ዋና ዳይሬክተር ኒጎዚ አኮንጁ አባልነቱን ለመቀላቀል ጥረት ከሚያደርጉት አገሮች መካከል ኢትዮጵያና ኡዝቤኪስታን ከፍተኛ የሆነ ተግባር የሠሩ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡
ኢትዮጵያ መሠረታዊ የሚል የድርድር ሒደትን በማከናወን ለአባልነቱ መቃረቧን የገለጹ ሲሆን፣ ያልተገደበ የፖለቲካ ቁርጠኝነት መኖሩ ተገልጿል፡፡ ኢትዮጵያ የደረሰችበት ወሳኝ ምዕራፍ የኢትዮጵያን ወደ አባልነት የመቀላቀል ሒደት ግልጽ ተስፋና እምነት መኖሩን የሚያመለክት ነው ተብሏል፡፡
ኢትዮጵያ አጠቃላይ ለአባልነቱ መሳካት ባለፈው አንድ ዓመት ብቻ ያደረገችው ጥረት ...

🔗 ተጨማሪ ያንብቡ: https://ethiopianreporter.com/153976/

----------||----------
የሪፖርተር ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን ይቀላቀሉ
ፌስቡክ ↠ bit.ly/2Iv9bZB
ትዊተር ↠ bit.ly/35qeNwV
ሊንክድኢን ↠ bit.ly/3S0k6uB
ኢንስታግራም ↠ bit.ly/44Iiuxb
ቴሌግራም ↠ bit.ly/3Qb4N1M
ዩቲዩብ ↠ bit.ly/3p0jUQY
ቲክቶክ ↠ bit.ly/3Ruxsyv
ትሬድስ ↠ bit.ly/466VBCG

🧾 የስራ ማስታወቂያዎች ↠ EthiopianReporterJobs.com
📢 የጨረታ ማስታወቂያዎች ↠ ReporterTenders.com

📩 ለዜና ጥቆማ እና መረጃ፡ [email protected]

✍️ ነጻ ፕሬስ፣ ነጻ ሐሳብ፣ ነጻ መንፈስ

29/03/2026

ኢትዮጵያ በቀይ ባሕር ጉዳይ ተመልካች ብቻ ሆና መቆየት አትችልም
********************

በአሁኑ ወቅት ዓለም ከአንድ ዋልታ ወደ ብዝኃ-ዋልታ የኃይል ሽግግር ውስጥ ትገኛለች። በዚህ የታሪክ አጋጣሚ ደግሞ የቀይ ባሕር ቀጣና የዓለም የጂኦ-ፖለቲካ ፉክክር ማዕከል ሆኗል።

ቀይ ባሕር ዝም ብሎ የውኃ አካል አይደለም፤ የዓለም ኢኮኖሚ "የደም ሥር" ነው።

በቀን በሚሊዮን የሚቆጠር በርሜል ነዳጅ የሚተላለፍበት ስልታዊ በር የሆነውን ባብ-ኤል-መንደብ እና አፍሪካን፣ አውሮፓን እና እስያን የሚያገናኝ የንግድ ድልድይ የሆነውን ስዊዝ ካናልን መቆጣጠር ለሀገራት የደኅንነት ዋስትና እና የኃይል ሚዛን የበላይነት ማረጋገጫ ሆኗል።

ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ያላት ታሪካዊ ቀጣይነት፣ የሕዝብ ቁጥር እና የዲፕሎማሲ ማዕከልነት የቀጣናው "ምሰሶ ሀገር" ያደርጋታል።

በመሆኑም ኃያላን በደጃችን ላይ ወታደራዊ መሠረት እየገነቡ ባለበት ሁኔታ፣ ኢትዮጵያ ተመልካች ብቻ ሆና መቆየት አትችልም።

በመካከለኛው ምሥራቅ ያለው አለመረጋጋት እና በቀይ ባሕር ላይ እየታየ ያለው ውጥረት፣ ኢትዮጵያ አስተማማኝ የባሕር መዳረሻ እንዲኖራት እና የባሕር ኃይሏን እንድታጠናክር የሕልውና ግዴታ ጥሎባታል።

የኢትዮጵያ ጂኦ-ፖለቲካዊ ስኬት የሚረጋገጠው በውስጣዊ መረጋጋት እና ጠንካራ ኢኮኖሚ፣ በአርቆ አሳቢ ዲፕሎማሲ እና ብሔራዊ ጥቅምን በሚያስቀድም አንድነት ነው።

ሀገራችን የራሷን የሕልውና መስመር በማበጀት፣ የቀጣናው የሰላም እና የንግድ ማዕከልነቷን በተግባር የምታረጋግጥበት ወቅት አሁን ነው።

የታሪካዊቷ ኢትዮጵያ ስልታዊ መነሣት በዝምታ የሚታለፍ ሳይሆን፣ የትውልድ አደራ እና የብሔራዊ ክብር ጉዳይ ነው!

ይህ ሐሳብ በሰፊው የተዳሰሰበትን መረጃ አስተያየት መስጫ ሳጥን ውስጥ ከተቀመጠው የድረ ገጻችን ሊንክ ያገኛሉ፦

Address

Addis Ababa
1000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Aseb/አሰብ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category